ካህኑን የአሜሪካው ፍርድ ቤት አገዳቸው፤
ሃገረ ስብከቱ በ30 ቀን ውስጥ መልስ ካልሰጠ ይፈረድበታል።
የቤተክርስቲያን አንድነትን ለመበታተን እየሰሩ ስለሆነ
ላልሰማ ያሰሙ!
የዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት ፤ የደ.ም.ቅ.ሚ.ካ የሚገኙ ጥቂት ካህናትና መነኮሳት እንዲሁም የማህበረ ቅዱሳን አባላት እና የሰንበት ት/ቤት አባላት በአንድ ላይ ተባብረው በዲሲና አካባቢወ ሀገረ ስብከት የሚገኙ አጥቢያ ቤተክርስቲያናትን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሃዋሪያዊ እና ሲኖዶሳዊ አስተዳደር ለመገንጠል እና በመናፍቃናዊ/በፕሮቴስታንት መዋቅር እንዲተዳደሩ ለማድረግ በዋሽንግተን ዲሲ ፍርድ ቤት ለማስወሰን እየተከራረከሩ ይገኛሉ።
ነገር ግን፤ ከዋናው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ቀን በፊት 01/13/2026እ.ኤ.አ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ፍርድ ቤት ሃገረስብከቱን ወክሎ የጠበቃነት ፍቃድ ሳይኖረው በማጭበርበር የቤተክርስቲያንን አንድነት ለመገነጣጠል ይከራከሩ የነበሩትን ካህን ህገወጥ ስራ እየሰሩ መሆኑን ፍርድ ቤቱ በማረጋገጥ ስለደረሰበት በማጭበርበር ላይ የነበሩትን ካህን ከዚህ በሁዋላ አጥቢያ ቤተክርስቲያናትን የመገነጣጠል ስራቸውን አንዳይሰሩ እና በሃገረ ስብከቱ በኩል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ለመገነጣጠል የገባውን ሰነድ ውድቅ በማድረግ ካህኑ ፍርድ ቤት ተገኝተው መከራከር እንዳይችሉ አግዶአቸዋል::
ፍርድ ቤቱም በ 30 ቀን ውስጥ ሃገረስብከቱ ለተከሰሰበት ክስ በጠበቃ የተደገፈ ሙሉ መልስ (እንዴት አድርጎ አጥቢያ በቤተክርስቲያናትን ከሃዋሪያዊና ሲኖዶሳዊ አስተዳደር ለመገንጠል እንዳሰበ) በጽሁፍ መልስ የማያስገባ ከሆነ ሀገረ ስብከቱ ላይ ፍርድ እንደሚፈረድበት ፍርድ ቤቱ ገልጾ ውሳኔ አሳልፎዋል።
ስለሆነም፡ ከፍርድ ቤቱ ቀነ ቀጠሮ በፊት ለመላ አገልጋዩችና ህዝበ ክርስቲያኑ ጉዳዩን ለማሳወቅ እና ሁሉም ቤተክርስቲያኑን ነቅቶ እንዲጠብቅ የፍርድ ቤቱን ጉዳይ ለማስገንዘብ ይህ ጉባኤ ተዘጋጅቶዋል።
LIVE
ላልሰማ ያሰሙ!
January 24/2026 Saturday 10:00AM ጠዋት
በዋሽንግተን ዲሲ አቆጣጠር
ለሁሉም ክፍት የሆነ የፍርድ ቤቱን ሁኔታ ለማስገንዘብ የቀጥታ ስርጭት ተዘጋጅቶዋል።
Loading...
Loading...
የጉባኤው መግቢያ
Join LIVEhttps://meet.google.com/mwj-udff-oop
To join by phone, dial +1 470-268-2285 and enter this PIN: 318 457 921#
ጉባኤው ለዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት በሃላፊነት ላይ ላሉ አባቶች ካህናት እንዲሁም ለሁሉም አገልጋይ ካህናት በየማእረጋቸው፤ በአለም ዙሪያ ለሚገኙ ምእመናን ፤ ለሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች፤ ለማህበረ ቅዱሳን አባላት ሁሉ ክፍት ነው።
የቤተክርስቲያን ድምጽ ለመሆን በእለቱ በኢንተርኔት ጉባኤውን በመሳተፍ የበኩልዎን ይወጡ